ለወንድሞቻችን እና እህቶቻችን በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች የተነገሩትን መልእክቶች ለመማማርና ለማስተላለፍ የጋራ ምንጭ ለመሆን እንጥራለን።
ራዕይ
ራዕያችን በማኅበረሰባችን ውስጥ ያለውን ታላቅ ተልእኮ ለመፈፀም እና በክርስቶስ በመኖር እና ፍቅሩን ለሌሎች ለማካፈል ነው። ለዚሁ አላማ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች የተነገሩትን መልእክቶች በመጠቀም ወንጌልን ማዳረስ።
እሴቶች
ከሐይማኖታዊ ልምምድ ይልቅ ክርስትና የሚያተኩረው በግንኙነት ላይ ነው። ይህን “አድርግና አታድርግ” የሚል መመሪያ ከመዘርዘር ይልቅ የክርስቲያን ግብ ከእግዚሐብሔር አባት ጋር የቀረበ ግንኙነት እንዲኖር ያበረታታል። ያ ግንኙነት እውን ሊሆን የቻለው በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራና መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያኑ ሕይወት በሚኖረው አገልግሎት ነው።አንድ ሰው ለመዳን ከፈለገ በመስቀሉ ላይ በተፈፀመው የክርስቶስ ሥራ እምነቱን ማኖር አለበት። ማንም ሰው ክርስቶስ በእርሱ ፋንታ እንደሞተና ለራሱ ኃጢያት ዋጋ እንደከፈለለት እንደገናም እንደተነሳ ካመነ፣ ያ ሰው ድነት አግኝቷል ማለት
ነው።
እምነት
ማንም ሰው ድነትን ለማግኘት ምንም ማድረግ አይችልም። ማንም ግለሰብ በራሱ
ወይም በራስዋ “መልካም በማድረግ” እግዚሐብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም። ምክንያቱም ሁላችንም ኃጢያተኞች ስለሆን።አንድ ሰው ለመዳን
ከፈለገ በመስቀሉ ላይ በተፈፀመው የክርስቶስ ሥራ እምነቱን ማኖር አለበት። ማንም ሰው ክርስቶስ በእርሱ ፋንታ እንደሞተና ለራሱ
ኃጢያት ዋጋ እንደከፈለለት እንደገናም እንደተነሳ ካመነ፣ ያ ሰው ድነት አግኝቷል ማለት ነው። (ኢሳያስ 53፡ 6፣ 64፡
6-7) ። ሁለተኛም ከዚህ የበለጠ የሚሰራ ሥራ የለም። ምክንያቱም ክርስቶስ ሁሉን ሥራ አከናውኖታል! በመስቀል ላይ ሆኖ ክርስቶስ
እንዲህ ብሏል “ተፈፀመ” (ዮሐንስ 19፡ 30) ።
No comments:
Post a Comment